Monday, December 15, 2014

                    ተደራጅ 2007 ለለውጥ
 



አንድነት በነገው ዕለት ተደራጅ 2007 ለለውጥ የሚል ዘመቻ በሶሻል ሚዲያና መዋቅሩ በዘረጋባቸው የሀገሪቱ አከባቢዎች ሁሉ ይጀምራል! የዚህ ዘመቻ ዓላማ በቀጣዩ ምርጫ ፓርቲው አሸናፊ ሆኖ አንዲወጣ የሚያደርጉት ህዝባዊ ንቅናቂዎች ለመፍጠር ያለመ ሲሆን፤ ህዝቡ በምርጫው ሂደት ከመጀመሪየው ጀምሮ ተሳታፊ እንዲሆን በፓርቲው በአባልነትና በደጋፊነት እንዲደራጅና በንቃት እንዲሳተፍ ያደርጋል። ህዝቡ ተደራጅቶ ታህሳ 12 በሚደረገው የህዝብ ታዛቢዎች ምርጫ ላይ ቤቀበሌው በመገኘት ገለልተኛ ሆኑና በህዝቡ ዘንድ ተአማሚነት ያላቸው የህዝብ ታዘቢዎች የመርጣል፤ በቀጣ ደግሞ የምርጫ ካርድ ሁሉም በነቂስ እንዲወስድ ይደረጋል፤ ከዚያ ድምፁ እንዳየጭበረበር የአንድነት ታዛቢ ሆነው የሚያገለገሉ ያዘጋጃል፤ በአጠቃላይ የምርጫው ሂደት በህዝቡ የነቃ ተሳጠፎ ተጀምሮ እስከመጨረሻ ድረስ የዘልቃል ማለት ነው። ይህ ሁሉ ተደርጎ ኢህአዴግ ተሸንፎ እያለ የህዝቡን ድምፅ ለማጠፍ የሚንቀሳቀስ ከሆነ አሁንም የተደራጀው ህዝብ ህዝባዊ እምቢተኘነት በማካሄድ ድመፁን እንዲያስጠብቅና የስርዓት ለውጥ ለማምጣት ይገዳል ማለት ነው።
 

አንድነት ይህን ትግል በአግባቡ ለመምራትና ይሄ ዓመት የኢህአዴግ መጨረሻ ለማደረግ ቆረጦ ተነሰተዋል። የህዝቡን ድምፅ በምንም ዓይነት ሁኔታ አሳልፎ የሚሰጥበት ሁኔታ አይኖርም፤ ህዝቡም ቢሆን ድምፁ እንዳይወሰድበት ካሁኑ ከፓርቲው ጎን በመቆም መደራጀትና በንቃት መሳተፍ ይኖርበታል።
                                                     ድል የህዝብ ነው!